መንበር
ናፋቂ ከያኒዎች!
ክፍል -፪
ባለፈ
ጊዜ በክፍል ፩
ጹህፌ ስለ መንበር ናፋቂ ሙዚቀኞ
የሚዚቃ ሥራና ሰትራቴጂያቸውን በማንሳት መንበርና መድረክ እንዴት
እንደሚያገኙ በወፍ በረር ለማስቃኘት ሞክሬ ነበር ፡፡ዛሬ የመንበር ፈላጊ ተዋንይን አካሄድን እንይ እስቲ፡፡
ተዋናዮቻችን እንደአሰላለፋቸው መደብ አውጥተን
በአራት ተርታ ብናሰልፋቸው ስዕል ለመስጠት የሚረዳ ይመስለኛል፡፡
1ኛ) ትኩረታቸውን ጥበቡ ላይ ብቻ በማድረግ ህብረተሰቡን
ያስከፋል ከሚሉት ተግባር በመቆጠብ የጥበብ ሥራ ለመስራት ብቻ የሚፈልጉ የተከበሩ ተዋናዮች፤
2ኛ) በተገኘው አጋጣሚ ገንዘብ የማግኘት፣ የመታየት አጋጣሚ
ወይም ላቅ ብለው ለመታየት መንበር የሚያገኙበትን ሁኔታ የሚቆፍሩ(የእነዚህ አካሄድ ቀጥታ ወደ መንግስት ጠጋ ጠጋ በማለት
ሳይጠራቸው አቤት ሳይልኳቸው ወዴት በማለት በተገኘው የመንግስት ንቅናቄ፣ የመንግስት መድረኮች
ላይ ተጋግጠው ፊጢጥ የሚሉና የሚረባ የማይረባ የከተፋ ሥራ በመስራት ገንዘብ የሚገኙበትን የሚያነጣጥሩ ናቸው፡፡)
3ኛ) በአብዛኛ በቲያትር ቤቶች ውሥጥ
ተቀጥረው የሚሰሩ በድርጅት አባለትንት በይፋ የሚታወቁ ምነዓልባት የድርጅት
አባል ለመሆን ፍላጎት የሌላቸው ላይ የአለቃነት መንፈስ የሚያሳዩና ስንጥር ከምታክል ስልጣን እስከ የአርቲስቱን የህይወት
አቅጣጭ የመቀየር አቅም ያለው ስልጣን ያላቸው እና የድርጅት አባልነታቸውንና አሰተኳሽነታቸውን
እንደ ብቃት (efficiency) በመጠቀም የከፍተኛ ትምህርት አጋጣሚን ጨምድደው የሚዙ ወይም ተጨማሪ ስልጣንየሚሹ ናቸው፡፡)
4ኛ) እነዚህ ደግሞ የሚተወን ነገር ወይም ገንዘብ ይገኝ
እንጂ ህብረተሰቡን ያስከፋል ወይም የወደፊት ህይወቴ ላይ ጥላሸት ይቀባል የማለት ግድ የሌላቸው ናቸው፡፡
በነገራችን ላይ አይናቸውን
በጨው አሽተው የተሰጣቸውን የሙያ ከበሬታ በመጠቀም
የካድሬ ስራ በመሥራት ከህዝቡ ልብ ውስጥ የወጡ፤ እና
ከህዝቡ ልብ ለመውጣት አፋፍ ላይ ያሉት ካልሆነ በስተቀር
በአብዛኛው ተዋንያን ከመንግስት ጋር የመጣበቅና
የፕሮፓጋንዳ አይነት ሥራ መስራት ወይም መንበር የመናፈቅ ፍላጎት አላቸው ለማለት አይቻልም ወይም በግርድፉ ተቀላቅለዋለ ቢባል እንኳን የነበረው ወይም ያለው ሁኔታ አስገድዷቸው ቢቸግር የተጣመሩ
ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ እስቲ መጠሪያ እየሰጠናቸው ባህሪቸውን
እንይ፡-
የቲያትር ቤት ፊት አውራሪዎች
እነዚህ ተዋንያን ገሚሱ ወንበር ያገኙ
ገሚሱ ወንበር እንዳያገኙ የተለያየ የቲያትር ቤቱ መስፈርት( የትምህርት ደረጃ ሊሆን ይችላል ) እንቅፋት የሆነባቸው ሲሆኑ፤
ይሁንና በተለያየየኢህዴግ የድርጅት መዋቅር ውስጥ ያሉ
በመሆናቸው ወንበር ከያዙት
ያላነሰ አቅም ያላቸው ሆነው የተለያየ ጥቅም
የሚያገኙ ናቸው፡፡ ስብሰባ፣ የፕሮፓጋንዳ ዝግጅቶች፣ የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትሩ ቀብር ማሰፈጸም፣ የንቅናቄ ስራ፣የብሄር ብሄረሰብ ዝግጅት ላይ አለን
አለን የሚሉ፣ ስም የሚመዘግቡ፣ አመራር የሚሰጡ፣ ፕሮግራም የሚያወጡ፣ ጉድጋድ ሳይቆፈር ቀድመው ችግኝ ተካይ ነንኝ የሚሉ፣በአውቶብስ
ውስጥ እየተጋፉ ከአወውቶብሱ ውጪ የጠቅላይ ሚንስትሩን ፎቶ ያለበት ያደፋ ከነቴሪያ የለበሰ የእምሮ በሽተኛ የአውቶብስ
ግፊያቸውን ትተው በሞባየላቸው ፎቶ ለማንሳት የሚንደፋደፉ፣ ሰው የሚያስተኩሱ፣ ባልተገራ አንደበታቸው ወይም የፊደል እጥረት ባለው አስተሳሰባቸው በቴለቪዥን ወይም በሬድዮ እነርሱን ፈትቶ የሚገጥማቸውን ህዝብ እንደዚህ ነው ማድረግ ያለብህ፣ እኛን ተመልከት፣ አትሳሳት ወዘተ..
እያሉ ከኛ ወዲያ ንቃት ሲሉ ይታያሉ፡፡
እነዚህ
አጋፋሪዎች አጋፋሪነታቸው የሚያተርፈው ጥቅሞች አሉት፡፡ የሰው ቲያትር
እነዲያልፍ ወይም እንዲወድቅ ጫና የመፍጠር አቅም፣ መድረክ
የመስጠት ወይም የማግኘት አቅም፣ የተደራደሩባቸው ፊልሞች ለዕይታ
እንዲበቃ የመወሰን ወይም የማስወሰን አቅም፣ የተለያየ አበል
ያላቸው ስልጠናዎች ማግኘት ወይም ማስገኘት፣ በፈለጉት ሰዓት የመንቀሳቀስ
ወይም የማንቀሳቀስ አቅም የተወሰኑት ናቸው፡፡
አንድ ጊዜ አንድ ቲያትር ቤት አንድ ተዋናይን ለሥራ
ጉዳይ ላናግር ቢሮው ቀጠረኝና እኔና አንድ ባልደረባዬ ወደ ተቀጠርንበት ቲያትር ቤተ ሄድን
ግለሰቡ ቢሮው ጋበዘንና የመጣንበትን ጉዳይን ስናወራው በየተወሰነ
የንግግራችን አንጓ ላይ 2ኛ ዲግሪየን ቲያትር ለልማት(theater for development) እየሰራሁ ስለሆነ
የሚለው ንግግር አሰለቸንና እኔና ባልደረባዬ አይን ለዓይን
ስንተያይ ቆይተን ከቢሮው ስንወጣ ጉዳያችንን ትተን ፤ አይ
ሁሌተኛ ድግሪ! ብለን እንኳን በድርጅት ጉያ ስር ተሸጉጦ በወጉ ሳይማሩ ለሚወሰድ ድግሪ ቀርቶ በአግባቡ በአለም አቀፍ ደረጃ
የተቀመጠለትን መስፈርትና የትምህርት ጊዜ በተገቢው ሁኔታ
ያለምንም ጥገኝነት ተከታትለው ሁለት ሶስት ድግሪ መያዝ በየሰዓቱ
እንደ ዳዊት የሚደገም ጉዳይ አይደለም አሁን አሁን! አልን፡፡ የሚገርመው ደግሞ! አለኝ
ባልደረባዬ፤ ይህ ሰው እኮ ተገቢውን የዩኒቨርስቲ መግቢያ ነጥብ
ሳያማሉ በማበረታቻ በዘመቻ ገብተው በዲፕሎማ ራሳቸውን
አማሙቀው ወደ ድግሪ በመከራ ከተዘዋወሩት ተዋናዮቻችን መሃል ነው አለኝ፡፡ እኔም ያም ሆነ ይህ
ወረቀት ይዞ መገኘት ነው አልኩት ወረቀት በሚናፈቅበት የትያትር
ቤት ምህዳር ውስጥ ሆኖ፡፡
ስለ አንድ የቲያትር ቤት አጋፋሪ ገጠመኝ አስነብቢያችሁ ከቲያትር ቤት ልውጣ፡፡ አንድ አንጋፋና በየፊልሞች ላይ
የማናጣው ተዋናይ አጋፋሪ ከመሆኑ በፊትና በኃላ
እራሱን በመስታወት ያየበትን ሁኔታ
ላጫውታችሁ፡፡ አርቲስቱ ወደ መኖሪያ ቤቱ ሲገባ በመኖሪያ ቤቱ አቅራቢያ ካለ መጠጥ ቤት አንድ
ሁለት እየለ የአካባቢው ወጣቶች እንደ መልካም መሪያቸው እያዩ ጋሽ እከሌ
ዛሬ እኔ ነኝ የምጋብዝ ፣ዛሬ እኔነኝ የምሸኝ እያሉ ዘና ብሎ በአጃቢ እቤተ የሚገባ ሰው ነበር ፤ ታዲያ ይህ አንጋፋ አርቲስት
የቤት ችግር አለበት ነበርና (ሁኔታው ኃላ ሲጣራ ነው)
የቤት ጉዳዩን ለመፍታት በድርጅት ታቅፎ ውሥጥ ለውስጥ በሰውር ንቅናቄ ሲያደርግ ቆይቶ የድረጅት ቁርጠኝነት የሚለካበትን፣
የህዝብ ተቀባይነትን ለስልጣን ማቆያ መጠቀም፤ በሚለው ስልት ለምርጫ እንቅስቃስው እጩ ተወዳዳሪ ሆኖ
ፎቶው በአካባቢው ይለጠፍና ምርጫው
ካለፈ በኃለ ይህ ለመሬት የከበደ ተዋናይ ግርማ ሞገስ ያለውን ጥቁርና ነጭ ጸጉሩን አሳምሮ አገር ሰላም ብሎ ያች ማታ ማታ ጎራ የሚልባት መጠጥ ቤት ገብቶ መጠጡን
መጠጣት ሲጀምር ከገባበት ጊዜ ጀምሮ ሁኔታውን በንቀት
ሲከታተሉ ከነበሩት ወጣቶች
አንዱ ከሚጠጣበት በደንምብ ፍላት ድንገት ብድግ ብሎ የተዋናዩን
እናት
አሰጠያፊ ስድብ በመሳደብ ምን ታየኛለህ ብሎ ሲያፈጥ፤
አርቲስቱ እርሱን የተባለ መሆኑን በመጠራጠር ፊቱን ወደ ኃላ
አዙሮ አጣርቶ በመመ ለስ እኔን ነው ያናገርከኝ ብሎ በማሳዘን ሲጠይቅ፤
ወጣቱ ጠረጴዛው ያለውን የመጠጥ ጠርሙስ በእጁ አፈፍ አድርጎ ሊወረውር ሲል አጠገቡ ያሉት ባልነጀሮች ገላገሉት፡፡ የመጠጥ ቤቱ
ባለቤቶች ምንድን ነው ነገሩ በምን ጊዜ ተነጋግራችሁ ነው
ብለው ለማጣራት ሲሞክሩ የወጣቱ ባልንጀሮች አርቲስት ነው ብለን ስናከብረው ለካ እስከ ዛሬ ሲሰልለን ነበር ብለው፤
በሁኔታው
ግራ የተጋባው አርቲስቱ ነገር ለማብረድ ወጥቶ ሲሄድ ሰላም
እንደተፈጠረ ሁኔታውን የተከታተለ አንድ ሰው ያጫወተኝ
ለፊት አውራሪ ተዋናዮች ክብር የሚሰጣችሁ ህዝብን የሚያከብር ስራ ስትሰሩ እንጂ መንበር ስትናፍቁ አይደለም የሚል መልዕክት ያስተላለፈ አጋጣሚ ነው፡፡
ባለድርጅትፊታውራሪ ተዋናዮች
እነዚህ በድህና ጊዜ በህዝብ ተወዳጅነታቸው በመጠቀም
ቶሎ ቶሎ ንብረት እና ድርጅት አፍርተው ከንብረታችን ወዲያ ያለ ህዝብ ለምኔ! በማለት
የመንግስት የተለያየ የቅስቀሳ መድረኮች ላይ ከባለስልጣኖች ፊት በመቆም ለአብዮቱ ዘብ የቆሙ መሆናቸውንና ታማኝነታቸውን
ያሰስመሰከሩ፣ የተለያየ ፕሮጀክት እየነደፉ የቁርጥ ቀን ልጅ
መሆናቸው የሚያሳይ የምስክር ወረቀት ከፕሮጀክታቸው ጋር ኣባሪ ደብዳቤ በማድረግ ገንዘብ የሚሰበስቡ ከህዝብ ልብ
ውስጥ መውጣታቸውን ልቦናቸው ስላወቀ በተለያየአጋጣሚ በቴሌቪዝን
መስኮት ብቅ በማለት ለተመልካች አሰልቺ ሥራ በመስራት አለው ምን ታመጣላችሁ!በሚል ስሜት ብር
የሚሰበስቡ የራሳቸውን ፊልም ከመንግስት ፖሊሲ ጋር በማገናኘት ማንነታቸውን ጠንቅቆ የሚያውቃቸው
ህዝብ ላይ እንደ አገር ወዳድና ገለልተኛ ኢትየጵያዊ የፈጠራ ታሪክ እየሰሩ ወይም በአምሳዮቻቸው ሙገሳ እያሰሩ፤ ይህንን በጥንቃቄ
የሚስተውላቸውን ህዝብ ላይ ከመድረክ ባሻር አርቴፊሻል ትወናበመተወን ወደ ሀብት ጉዞ የሚጋልቡ
ናቸው፡፡ ባለ ድርጅት ፊታውራሪዎች ፊልም ከሰሩ ለምረቃታቸው የሚያገለግል የመሰብበሰቢያ አዳራሽ መደበኛ ፕሮግራም የማሰረዝ ደንብና መመሪያ ጥሶ የእነርሱ
ዝግጅት እንዲካሄድ የማድረግ አቅም አላቸው፣ በአገሪቱ በየትኛውም አቅጣጫ
የሚካሄዱ ቴሌቶኖች ላይ አስታዋዋቂና መድረክ መሪዎች ናቸው፡፡ ከሚሰበሰበው ገንዘብ
በፐርሰንት እነርሱና ሙሰኛ የቴሎቶን ኃላፊዎች ጋር በሚያደርጉት ከመጋረጃ ጀርባ
ድርድር ለክልሉ ልማት ተጨናቂ በመምሰል የብሄሩን አልባሳትና ቁሳቁስበመጠቀም ከራሱ ከለፈፉለት ህዝብ በሚልየን በገዛ
እጃቸው የሚወስዱ ናቸው፡፡
አንድ የማስታወቂያ ባለሞያ የሆነ ሰው አንድ ጊዜ
ወደ በደ/ብ/ብ/ህ/ክልላላዊ መንግስት አንድ ዞን ላይ የወጣት ማዕከል ለመገንባት ከዞኑ ባላስሥልጣናት ጋር ከሚገኘው ገቢ በእርሱ
ሥም ለእነርሱም ጭምር ኮሚሽን እንዲይዝላቸው መደበኛ ባለሆነ(unofficial) መልኩ በመደራደር መደበኛ የሆነ
ውል ተዋውለው ሥራ ይጀመራሉ፡፡ ታዲያ ሥራው ከአዲስ አበባ ወደዚሁ ዞን በግል መኪና በመመላለስ
ለማስታወቂያ ሥራ የዞኑን መልካምድርና አይን ገብ የሆኑ ቦታዎችን በመቅረጽ ተግባራዊ እንቅስቃሴ አድርገው ለሥራ ማካሄጃ ከዞኑ
የሚጠበቀውን ብር ልቀቁልን በሚል በዚህ ጉዳይ ላይ ቀጠሮ እየያዙ
በመነጋገር ላይ እያሉ በዞኑ ላይ ልዩ ግምገማ ተያዘ ተባለና ግምገማው እስኪጠናቀቅ ለተወሰነ ጊዜ የተግባሩ እንቅስቃሴው ተቋርጦ
ግምገማው ሲጠናቀቅ ይህ ደንበኛዬ ከግምገማው በኃላ የሥልጣን
ማሸጋሸግ ተፈጥሮ ነበርና ቀደም ሲል በድርድሩ ውስጥ
የነበረና በግምገማው የተሻለ መንበር ያገኘውን ሰው ጉዳያችን ምን ደረሰ ብሎ ሲጠይቀው የተለያየ ምክንያት ሲያቀርብና ሳምንት፣ አሥራ አምስት ቀን ሲቀጥራቸው ቆይቶ እነዚህ የቁርጥ ቀን
መሆናቸውን የሚያሳይ አባሪ ደብዳቤ የያዙ ባለ ድርጅት
ፊታውራሪዎች ከሆኑት መካከል አንደኛው የተሻለ መደራደሪያ አቅርቦ የነጠቃቸው
መሆኑን ነግሮኝ ከዞኑ አስተዳደር ጋር የተዋዋለበትን
ውል ይዞ የህግ ምክር የጠየቀኝን ሰው አስታውሳለው፡፡
ታዳጊ (the up coming)ፉት አውራረሪ ተዋናዮች
እነዚህ
ተዋናዮች ወጣቶች ወይም የወጣትነት ዕድሜ ላይ ያሉ
ሲሆኑ፤ ቀደም ሲል የድርጅት ባለቤት ፊታውራሪ የሚባሉ ተዋናዮችን
አርአያ በማድረግ የሚንቀሳቀሱ ሲሆኑ ከቀደሞቹ ለየት
የሚያደርጋቸው በገንዘብ አቅም ያልጎለበቱ መሆናቸው፣
ወጣት መሆናቸው፣ ምንአልባትም ስም ያለው ወይም የገንዘብ አቅም
ያለው ድርጅት የሌላቸው በመሆናቸው፣ አካሄዳቸው እነደቀድሞዎቹ
ፍጥነቱን ጠብቆ በማለሳለስ ፊት አውራሪነታቸውን የተቆናጠጡ ሳይሆን ፤ፈጣጣ የሆነ ችኩልነት የሚያሳዩ(ከጠቅላይ ሚንስትሩ ወይም ከመከላከያ ሚኒስትሩ አጠገብ አይናቸውን በማፍጠጥ ፊጢጥ ብለው
ሊያነብንቡ የሚችሉ ወይም የጥበብ ሰው ነኝ አድናቂዎቼ ከፖለቲካ
መሪዎቹ ጋር ያመሳስሉኛል(Associate) ያደርጉኛል ብለው ጥንቃቄ የማያደርጉ ወይም እንደዚህ የማይገባቸው ናቸው፡፡ስልጠናና
ከፍተኛ ትምህርት የሚያገኙበትን ቀዳዳ የሚፈልጉ ወይም የሚጠቀሙ፣ ልታይ ልታይ የሚሉ ለንግግራቸው ዜማና ቃና የሚፈጥሩ
እራሳቸውን እንደ ጋዜጠኛ እንደ መድረክ መሪ የሚያደርጉ መንበር ናፋቂነታቸውን በቀላሉ ስማቸው ሊታወቅ
የማችሉ የመንግስት ኃላፊዎችን ነባር ታጋዮችን እስከ አያታቸው
ስም በመጥራት ነጥብ ማስመዝገባቸውን ማረጋገጥ የሚፈልጉ፤ በታላላቅ እና እኩያ የሞያ አጋሮቻቸው
ፊት ላይ ያለምንም ይሉኝታ ዘለል ዘለል የሚሉና የሚዘባነኑ! ከእነእርሱ ወዲያ ሰው ያለ የማይመሰላቸው ፣የተለየ
መብት(Immunity) ያለቸው የሚያስመስሉ፣የተለያዩ ዝግጅቶ(ፊልም ምረቃ፣ቲያትር ምረቃ፣ መጽሀፍ ምረቃ ወዘተ ላይ አጋፋሪ
የሚሆኑ የመንግስትየሚመለከታቸው አካላቶች እንደ ጋደኞቻቸው ሊጠሩ እንደሚችሉ ስልካቸውን እያሳዩ የሚያሰወሩ) አዋቂነኝ አይነት
ስታየል የሚያሳዩ፣ ሬድዮ ፕሮግራሞች ሊሰሩ የማይመለሱና ራሳቸውን
እንደ አስተማሪ የሚጠቀሙ ወይም በሚሰሩት ዝግጅት ላይ ቀጥተኛም
ሆነ ቀጥተኛ ባልሆነ መልኩ ሊጠቅማቸው የሚችለውን ኃላፊ የሚጋብዙ፣ቴሌቪዥን ወይም ሬድዮ ፕሮግራሞች አለያም የመድረክ ዝግጅቶች
ከሞያ ባለደረቦቻቸው አፍ ላይ ነጥቀው ያለምንም ይሉኝታ የሚናኙበት፣እነርሱ
ከተሰማሩበት ሞያ ጋርና ከመንግስት ጋር የማያግባባ ጉዳይ ወይም ሊያስከፋ የሚችል የመንግስት ህፀፅ የማይነኩ
ናቸው፡፡
ታዳጊ
ፊታውራሪ ተዋናዮች አጋጣሚ የሚሹ(opportunity seeker)
ናቸው፡፡ አሰተሳሰባቸው ህዝብ እንዲያደንቀን ወይም እንዲያከበረኝ ልሥራ ሳይሆን የገዢው መንግስት ቱባ ባለሥላጣኖች
እንዲደንቃቸው ወይም ታዛዥነታቸውንና ቁርጠኝነታቸውን
እንዲመዘግቡላቸው ነው የሚሹት፡፡ ለዚህ ዓላማቸው የሚረዳቸው ህዝብና መንግስት የማይገባባቸው አጀንዳዎች ላይ
መንግስት ዝግጅት ቢያዘጋጅ ዘለው መድረክ ላይ ፊጥ የሚሉ ፊታውራሪዎች እነርሱ ሆነው ፤ የዚህ ሥራ ባለቤት የሆኑት ካድሬዎቹ ሳይቀር ሥራቸውን
ከእነሱ እጥፍ በሆነ መልኩ ሲሰሩላቸው አይተው አፋቸውን ከፍተው
እንዲያያቸው ያደርጋቸዋል፡፡
ስለ
ህዝብና ስለ ስም መጠልሸት ስለ ህሊናዊነት ግድ የሌላቸው እውቅናና ገንዘብ
ብቻ ወደፊት የሚሉ ተዋናዮች
እነዚህ
ተዋናዮች ዋነኛ ዓላማቸው ትወናቸውን መስራት ፣ገንዘብ
ማግኘት፣ በህዝቡ ተደንቀው መታየት(ማነታቸውን በማያውቁ ሰዎች ወይም በእነርሱ ቢጤ አድናቂዎቻቸው(በተለይ ሴቶች) ልብ ስር
መንገስ)፣ አንድ ቦታ ተመሽገው ስለ ሰው እያወሩ ሲጋራቸውን ማጨስ ጫታቸውን ማመንዠግ ጨብሲያቸውን አቅም ያላቸው አልኮል መጠጥ የሚጋቱ አቅም
የሌላቸው ደግሞ ድራፍታቸውን ወይም ሃረቄያቸውን እየጨለጡ በስተመጨረሻ ሲመሻሽ ወይ ሲነጋባቸው ክብር የሰጣቸውን ህዝብ ክብር
የሚነሱ፣ ስለ ስማቸው መጠልሸት፣ስለ ለህዝብ ምንይለኛልና
የሚሰሩት ሥራ ከሚያደንቃቸው ህዝብ ጋር የሚያጋጭ ነው አይደለም፤ ግድ የማይሰጣቸው፣ በሚያዩት የህዝብን የመንግስት ቁርቁስ ሙድ የሚይዙ ፣ ማህበራዊ ኃላፊነት የማሰማቸው ፣ ኃላፊነት የሚሰማቸው
ከያኒዎችን የሚተቹ፣ መሻሻል የማይታይባቸው ሁል ጊዜ የሰው
ተቀጣሪ የሚሆኑ ፣ ስልጠና ከፍተኛ ትምህርት ታሪካዊ ጠላታቸው
የሆነ፣ መኪና መያዝ የምተዓመቱ ግባቸው የሆኑ ናቸው፡፡ በእርግጥ
እነዚህ ተዋናዮች መንበር የመናፈቅ ዕቅድ
በማስታወሻቸው ላይ ያልሰፈረ ቢሆንም ለመንበር ናፋቂዎች ምርኩዝ እየሆኑ የመንበር ናፋቂዎችን ቁጥር
ይጨምራሉ፡፡
የህዝብ ልብ መንበራቸው የሆነና ለህሊናቸው ና ለጥበብ
የሚሠሩ የተከበሩ ተዋናዮች
እነዚህ ተዋናዮች የሚሰሩትን ሥራ የሚያውቁ ፣ከህዝብ ጋር
የሚያጋጭ ሥራ የትየለሌ ገንዘብ የሚያስገኝ ቢሆን እንኳን በጭራሽ
አያፈልጉም፣የጥበብበ ሥራ ሊሰሩበመጀመሪያ ቅድመ ሁኔታቸው ከሞያ
አፍቃሪያቸው ጋር የማያጋጫቸው መሆኑንና ደረጃውን የጠበቀ መሆኑን ነው፣ እምብዛም ባለንብረትና ከፍተኛ የሆነ የገነዘብ አቅም የላቸውም፣ ሥማቸው በህዘቡ ውስጥ ከፍተኛ ቦታ ያለውና አብረቅራቂ
ነው፣የሥልጣን መንበር አይፈልጉም ወይም ለእነርሱ ምንማቸው
ነው፣ አጋጣሚ ካገኙ የህዝቡን ስሜት ና ብሶት የሚያሳዩ ወይም የሚገልጹ ሥራ መስራት ያረካቸዋል፣ ለሞያ እኩዩቻቸው ከፍተኛ ከበሬታ አላቸው፣ መንበር ናፋቂዎች ሆኑ ከታፊ ተዋናዮች ከፍተኛ አድናቆት
ይቸራቸዋል፣ የመንግስት ባለሥላጣናት በልባቸው ከበሬታ ይሰጣቸዋል፣ አብዛኞቹ አጉል ሱስ የለባቸውም ፣ ነውርና ሞራል
ይገባቸዋል፣ ሃይማኖታቸውን ያከብራሉ ጠንከር ያሉት ደግሞ ፃሚ፣ ፀላዮች ናቸው፣
ማህበራዊ ኃላፊነት ይሰማቸዋል፣ ደስተኛ ህይወት ነው የሚኖሩት፣ ለቤተሰቦቻቸው ከበሬታ አላቸው፣ትዳራቸው ወይም ለፍቅር ጋደኞቻቸው ታማኝ ናቸው ፣ ሰውን
በክፋት ማንሳት አይወዱም፣ ሀብት ለማግኘት ብለው ሰይጣናዊ
ቦታዎች አይሄዱም፣ የሰላም እንቅልፍ ይተኛሉ ፡ወዘተ…..
አንባቢያን እንግዲህ ለዛሬ የተዋናዮቻችንን እንቅስቃሴ
በምድብ፤ በምድብ አስቀምጠን እንዲሁም ባህሪያቸውን፣ ተግባራቸውንና ዓላማቸውን በጥቂቱ ለማሣየት ሞክሬያለው፡፡ ስለ ተዋናዮቻችን አካሄድ ብዙም
ላልተገለጸላቸው አድናቂዎች ምስል የሚከስት በተጨማሪ ደግሞ
እራሳቸው የአገራችን ተዋንያንን ምድባቸው እንዲለዩ ያደርጋል ብዬ እገምታለው፡፡ በሚቀጥለው ጊዜ አንድ ተጨማሪ የመንበር ናፈቂ ከያኒዎች ሞያን እንቅስቃሴ በማስነበብ ጹህፌን አጠናቅቃለው፡፡ መልካም ሁኑ፡፡